5. ሙሴ ስለ እስራኤል ሕዝቦች ያደረገውምልጃ፡ -
- ሕዝቡ የወርቁን ጥጃ አምልከዋልና እግዚአብሔር ሕዝቡን ሊያጠፋ ፈለገ፡፡
- ሊያደርገው የፈቀደውንም ቀጥታ አልፈጸመውም ለወዳጁ ለነቢዩ ሙሴ አማከረው፣ ስለ
ሕዝቡም ያማልድ ዘንድ እድል ሰጠው፣ ሙሴም በእድሉ ተጠቅሞ አማለዳቸው
እግዚአብሔርም ተቀበለው፡፡
- “እግዚአብሔርም ሙሴን፦ ከግብፅ ምድር ያወጣኸው ሕዝብህ ኃጢአት ሠርተዋልና ሂድ፥
ውረድ። ካዘዝኋቸው መንገድ ፈጥነው ፈቀቅ አሉ ቀልጦ የተሠራ የጥጃ ምስል ለራሳቸው
አደረጉ፥ ሰገዱለትም፥ ሠዉለትም። እስራኤል ሆይ፥ እነዚህ ከግብፅ ምድር ያወጡህ አማልክትህ
ናቸው አሉ ሲል ተናገረው። እግዚአብሔርም ሙሴን፦ እኔ ይህን ሕዝብ አየሁት፥ እነሆም
አንገተ ደንዳና ሕዝብ ነው። አሁንም ቍጣዬ እንዲቃጠልባቸው እንዳጠፋቸውም ተወኝ
አንተንም ለታላቅ ሕዝብ አደርግሃለሁ አለው። ሙሴም በእግዚአብሔር በአምላኩ ፊት ጸለየ፥
አለም። አቤቱ፥ ቍጣህ በታላቅ ኃይልና በጽኑ እጅ ከግብፅ ምድር ባወጣኸው በሕዝብህ ላይ ስለ
ምን ተቃጠለ? ግብፃውያንስ። በተራራ መካከል ሊገድላቸው፥ ከምድርም ፊት ሊያጠፋቸው
ለክፋት አወጣቸው ብለው ስለ ምን ይናገራሉ? ከመዓትህ ተመለስ፥ ለሕዝብህም በክፋታቸው
ላይ ራራ። ዘራችሁን እንደ ሰማይ ከዋክብት አበዛለሁ፥ ይህችንም የተናገርኋትን ምድር ሁሉ
ለዘራችሁ እሰጣታለሁ፥ ለዘላለምም ይወርሱአታል ብለህ በራስህ የማልህላቸውን ባሪያዎችህን
አብርሃምንና ይስሐቅን እስራኤልንም አስብ። እግዚአብሔርም በሕዝቡ ላይ ሊያደርግ ስላሰበው
ክፋት ራራ።” ዘፍጥ 32፡7-14፡፡
No comments:
Post a Comment